21. ይምበርበሩ ምትኬ ገብረጻድቅ YIMBERBERU MITIKE GEBRETSADIK
ተወዳጅ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን የሚድያ ሰዎችን ታሪክ ከአንጋፋ እስከ ወጣት በሚል ሀሳብ የብዙዎችን ታሪክ እያሰባሰበ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ወደፊትም የባለሙያዎች ታሪክ ራሱን ችሎ ደረጃውን በጠበቀና ጠንካራ በሆነ ሽፋን/hard
cover/ ኢንሳይክሎፒዲያ
ሊታተም
እንደሆነ
ይታወቃል፡፡
እስከዚያ
ድረስ
ታሪካቸው
በዚህ
ዊኪፒዲያ
እና በተወዳጅ ሚድያ የፌስ ቡክ ገጽ ላይ ከሚነገርላቸው መካከል የስፖርት ጋዜጠኛው ጋሽ ይምበርበሩ ምትኬ ይጠቀሳል፡፡
ጋሽ ይምበርበሩ ምትኬ ፕላዛ ሆቴል አካባቢ በሚገኘው ቤቱ የጡረታ እድሜውን እያሳለፈ ይገኛል፡፡ ጋሽ ይምበርበሩ ሊረሳ የማይገባ ጋዜጠኛ የብዙዎች ባለውለታ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡ በኦን ላይን ሚድያ ለመጀመሪያ በሚባል መልኩ የጋሽ ይምንበርበሩን ታሪክ አጠር ባለ መልኩ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡ ጋሽ ይምበርበሩን ለማስታወስ ምክንያት የሆኑን አቶ ሀይሉ ወልደጻድቅና
ልጃቸው
እመቤትን
ማመስገን እንወዳለን፡፡ በተለይ ጎግል ፎቶዎች ላይ የጋሽ ይንበርበሩን አንድም ምስል አላገኘንም ነበር፡፡ አሁን ከዚህ ጽሁፍ ጋር የጋሽ ይምበርበሩን የሚድያ ጉዞ የሚያሳዩ ፎቶግራፎችን
ወጥተዋል፡፡
ተወዳጅ
ሚድያ
ላልተነገረላቸው
እንቁም
፤ ላልተዘመረለት እንዘምር፤ የሰሩ ይታወቁ የሚል መርሁን ተግባራዊ ለማድረግ እነሆ የጋሽ ይንበርበሩን ታሪክ ታነቡ ዘንድ ጋበዝን፡፡
ልጅነት
በስፖርት ጋዜጠኝነቱ ሁላችንም የምናደንቀው ጋሽ ይምበርበሩ ምትኬ ዘንድሮ በ81 አመቱ ላይ ሆኖ ያሳለፈውን ወርቃማ ጊዜ ያስታውሳል፡፡ ጋሽ ይንበርበሩ በሰሜን ሸዋ በመርሀቤቴ ወረዳ በቡርቃቶ ገበሬ ማህበር በ1932 የተወለደ ሲሆን በአካባቢው በነበረው ባህል መሰረትም ቄስ ትምህርት ቤት ገብቶ ፊደልን ቆጥሯል፡፡ ወላጅ አባቱ አቶ ምትኬ ገብረጻድቅ እናቱ ደግሞ ወይዘሮ በስሙ ተስፋ ይባላሉ፡፡
ታዳጊው ይምበርበሩ ምትኬ 9 አመት ሲሆነው በ1941 መሆኑ ነው የእናቱ ታናሽ ወንድም ዘንድ አዲስ አበባ መጣ፡፡ አዲስ አበባ መጥቶም በቅዱስ ዮሀንስ ቤተ-ክርስቲያን ንባብ እየተማረ ሳለ በአመቱ መጨረሻ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን ወደምታስተዳድረው
ኮልፌ
ሰዋስው
ብርሀን
ተማሪ
ቤት በአዳሪነት ገባ፡፡ እዚያም መደበኛ ትምህርትን ተከታትሎ 5ኛ ክፍልን ጨረሰ፡፡ በ1947 መስከረም ወር ላይ ሲዳሞ ክፍለሀገር በይርጋለም ከተማ በኖርዌጅያን ሚሲዮን መምህራን ማሰልጠኛ ለ 2 አመት ተምሮ ተመርቋል፡፡ በጋሞጎፋ ክፍለሀገር በኮንሶ ወረዳ ሚሲዮን በሚያስተዳድረው
ት/ቤት ለአንድ አመት አስተምሯል፡፡
ትምህርትና ስራ
ይምበርበሩ ምትኬ ከፍተኛ የትምህርት ጥማት ስለነበረውም በ1949 መጨረሻ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ በመድሀኒአለም ባላባት ተማሪ ቤት ከ8ኛ -12ኛ ክፍል አጠናቅቋል፡፡ በ1956 አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቢዝነስ ፋክልቲ ለአንድ አመት ከቆየ በኋላ ትምህርቱን አቋረጠ፡፡ የኢትዮጵያ መካነ-ኢየሱስ ቤተ-ክርስቲያን ታስተዳድረው በነበረው የምስራች ድምጽ ሬድዮ በልጆች ክፍለ-ጊዜ አዘጋጅነት ተቀጠረ፡፡
በዚያ
መስሪያ
ቤት በልጆች ፕሮግራም አዘጋጅነቱ ሳይወሰን በልዩ ልዩ ፕሮግራሞች ላይ በመሳተፍ እስከ 1966 ድረስ ሰርቷል፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ፍላጎቱን ለመቀጠል እንዲያመቸውም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች አስተዳደር ክፍል ለአንድ አመት ተኩል አገልግሏል፡፡
ወደ ሚድያ አለም፡፡
በ1967 ወደ ማስታወቂያ ሚኒስቴር ተዛውሮ በሬድዮ መምሪያ በጡረታ እስከተገለለበት እስከ 1986 ድረስ በስፖርት ፕሮግራም ዋና አዘጋጅነት አገልግሏል፡፡ የተመደበበትን ስራ በብቃት መወጣት ይችል ዘንድም በ1960 በሬድዮ ፕሮግራሞች አጻጻፍ ስልት በናይሮቢ ኦል አፍሪካን ቸርችስ ለ4 ወራት ተከታትሎ ሰርተፊኬት አግኝቷል፡፡ በ1977 ደግሞ በቼኮዝሎቫኪያ ጋዜጠኝነትን በተመለከተ ተምሮ ዲፕሎማ ሊያገኝ ችሏል፡፡
ጋሽ ይምበርበሩ አጠቃላይ በሚድያ ስራ ከ29 አመት በላይ ያገለገለ ሲሆን 19 አመቱን በስፖርት ጋዜጠኝነት አገልግሏል፡፡ እንደ ደምሴ ዳምጤ ያሉ ጋዜጠኝነት ሙያ እንዲመጡ ትልቁን ድርሻ የተወጣው ጋሽ ይምበርበሩ ነበር፡፡
10ኛው
የአፍሪካ
ዋንጫ
ውድድር
በ1968
ሲከናወን
የውድድር
ዝግጅቱ
የተቃና
እንዲሆን
ጋሽ ይምበርበሩ የጎላ ሚና ነበረው፡፡ ለዚህም አስተዋጽኦው የክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ፊርማ ያረፈበት የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቶለታል፡፡
ክቡር
አቶ ይድነቃቸው ተሰማ የአለም እግር ኳስ ውድድር ተከናውኖ እንዳበቃ መግለጫ ወይም በጨዋታው ላይ የእንዴት ነበር ትንታኔ ይሰጣሉ፡፡ በዚህ ትንታኔ ላይ ጋሽ ይምበርበሩ ምትኬ በመታደም ስለ ጨዋታው አስፈላጊ እና ወሳኝ ጥያቄዎችን ያቀርብ ነበር፡፡
አደራ ተቀባዩ ጋሽ ይንበርበሩ
ወይዘሮ መንበረ ግርማ ከጋሽ ይምንበርበሩ ጋር የቅርብ ዘመድ ናቸው፡፡ ይንበርበሩ ትልቅ ውለታ የዋለልኝ ድንቅ ሰው ነው የሚሉት ወይዘሮ መንበር ልጄን ወልጄ ከ8 ወሯ ጀምሮ አሳድጎ ለቁምነገር ያበቃልኝ ነው፡፡ ለዚህ ውለታውም ዝንተ-አለም አመሰግነዋለሁ ሲሉ ሀሳብ ሰጥተዋል፡፡
ወይዘሮ መንበረ ጋሽ ይንበርበሩን ሲገልጹት ‹‹ እጅግ ቆፍጣና ብሎም ቆጠብ ያለ ይሉታል፡፡ ጋሽ ይንበርበሩ ሰው ሲያዝን ደራሽ ነው፤ ሰው ህመም ሲገጥመው ቀድሞ ተገኝቶ መላ ያበጃል፡፡ በዚህ ባህሪው በብዙዎች የተወደደ እንደሆነ ወይዘሮ መንበረ ይናገራሉ፡፡
የግንባር ስጋ
የቀድሞ ጋዜጠኛ እና ድምጻዊ ግርማ ነጋሽ ደግሞ በ1968 ግድም ጋሽ ይንበርበሩ ጋር መተዋወቁን ይናገራል፡፡ ከዚያም በ1972 የኢትዮጵያ ሬድዮን ስፖርት ክፍልን ሲቀላቀል ዋና አዘጋጆ ይንበርበሩ ምትኬ ነበር፡፡
‹‹ ጋሽ ይምርበሩ ሁላችንንም ስነ-ምግባር ያስተማረን ሀቀኛ ጋዜጠኛ ›› ሲል ግርማ ነጋሽ ለቀድሞ አለቃው ያለውን አድናቆት ይገልጻል፡፡
ግርማ እንደሚናገረው ይንበርበሩ ኳስ ሲዘግብ የተመለከተውን ነገር ብቻ ይዘግባል፡፡ ለእውነት የቆመ የስፖርት ጋዜጠኛ መሆኑን ብዙዎቹ ያውቃሉ፡፡ አለባብሶ ማለፍ የሚባል ነገር ይንበርበሩ ጋር አይሰራም፡፡ ብዙዎች በዚህ ባህሪው የግንባር ስጋ ሲሉ ስም ያወጡለታል፡፡
ጋሽ ይምበርበሩ ስራውን ካከናወነ በኋላ ቀጥታ ወደ ቤቱ ነው፡፡ ግርማ እንደሚያስታወሰው ‹‹ ይንበርበሩ ጭምት ነው፤ ቆጠብ ያለ ነበረ፡፡ ቀልድና ጨዋታ ጀምረን ከሆነ እርሱ ሲመጣ በዝምታ እንሞላለን፡፡ ከአክብሮት ጋር፡፡ ጋሽ ይንበርበሩ ቆጠብ ያለና ብዙም ቀልድ ነገሮችን የማይወድ በሚሰራው ስራ ላይ ብቻ አጽንኦት የሚሰጥ ሰው ነው ›› ሲል ግርማ ነጋሽ ይገልጸዋል፡፡
ምሩጽ ይፍጠር በሞስኮ ኦሎምፒክ ባሸነፈ ጊዜ ዘገባውን ያስተላለፈው ጋሽ ይምበርበሩ ምትኬ በኢትዮጵያ የስፖርት ጋዜጠኝነት ታሪክ ውስጥ ትልቅ አሻራ ካኖሩት ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ጋሽ ይንበርበሩ የተከበረ ታላቅ ሰው፡፡
መዝጊያ ፤ ይህ መዝጊያ የተወዳጅ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን አቋም የሚንጸባረቅበትና
የተወዳጅ
ዊኪፒዲያ
ቦርድ
አባላት
ከስምምነት
የደረሱበት
ነው፡፡
ኢትዮጵያ የሚከበሩ ሰዎች እያሏት ሰው ማክበር አታውቅም፡፡ በቀጥታ የሚድያ ሰዎች የተረሳን ከማስታወስ ይልቅ የታወቀን ያሳውቃሉ፡፡ ታዋቂዎች ብቻ የሚድያ ሽፋን ያገኛሉ፡፡ የሰሩቱ ግን ስለተደበቁ ወይም የሰሩ ስለማይመስል ታሪካቸው ወጥቶ መማማሪያ አይሆንም፡፡ ባለውለታ መዘንጋት ልማዳችን እየሆነ ከመጣ ሰነበተ፡፡ ጋሽ ይንበርበሩ መዘከር ያለበት ሰው ነው፡፡ ታሪኩ መጻፍ ያለበት ሰው ነው፡፡ እነ ደምሴ ዳምጤ ይንበርበሩ ነው ለዚህ ደረጃ ያበቃን ሲሉ በተደጋጋሚ ይደመጣሉ፡፡ ግን እንዴት የጋሽ ይንበርበሩን ታሪክ በትንሹ ማውጣት ሳይቻል ቀረ? ጋሽ ይንበርበሩ ድንቅ ሰው ነው፡፡ ታሪኩን በማውጣት በኩል የቅርብ ቤተሰብ ትልቅ ሃላፊነት እንደተጠበቀ ሆኖ ግለ-ታሪክን ቆፍረው የሚያወጡ አዳኝ የግለ-ታሪክ አጥኚዎች የግድ ያስፈልጋሉ፡፡እነዚህ
የግለ-ታሪክ አጥኒዎች በብዙ ቁጥር በየጓዳው ያሉ ለሀገር የደከሙ ሰዎች ወደ መድረኩ ብቅ በማለት ልምዳቸውን ማካፈል ይጀምራሉ፡፡ ለጋሽ ይንበርበሩ መልካም ጤንነት እየተመኘን ወደ ፊትም ሰፋ ያለ መጣጥፍ ይዘን እንደምንቀርብ ቃል እንገባለን፡፡/
ይህ ጽሁፍ የምርምር የቃለ-መጠይቅ እና የአርትኦት ስራው በጋዜጠኛ እዝራ እጅጉ የተከናወነ ሲሆን ዛሬ መስከረም 23
2014 በዊኪፒዲያ
ላይ እና በተወዳጅ ሚድያ የፌስ ቡክ ገጽ ላይ ወጣ፡፡/
አስተያየቶች
አስተያየት ይለጥፉ