ልጥፎች

ከጁን, 2022 ልጥፎች በማሳየት ላይ
ምስል
                         187ክብሬ ተስፋዬ አበበ       በታላላቅ ሁነት አዘጋጆች የምትመረጥ ባለሙያ   ተወዳጅ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን በሚድያ ዘርፍ ለሀገራቸው አንድ አሻራ ያኖሩ ሰዎች እየሰነደ ለመጪው ትውልድ እያስቀመጠ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ከ1950 ጀምሮ በየዘመኑ በሀገሪቱ የሚድያ ኢንዱስትሪ ውስጥ ገብተው የራሳቸውን ቀለም ፈጥረው የተገኙ ሰዎችን ከያሉበት ፈልገን የህይወት ታሪካቸው እንዲታወቅ ፤ ራሳቸውም ራሳቸውን እንዲያውቁ ወደ ኋላ መለስ ብለው ምን አበርክቼ ይሆን እንዲሉ መንገዱን እያመቻቸን ነው፡፡ መዝገበ-አእምሮ የ180 የሚድያ ሰዎች ታሪክ የሚለው ባለ 600 ገጽ መጽሀፋችንም ሀምሌ 30 2014 በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቴአትር ይመረቃል፡፡   ታሪካቸው በዊኪፒዲያ፤ በተወዳጅ ሚድያ ድረ-ገጽና በልዩ ልዩ መንገድ ከሚሰነድላቸው ብርቱ የሚድያ ሰው ፤ የመድረክ መሪ የኮሚኒኬሽን ባለሙያ   የሆነችው ክብሬ ተስፋዮ ናት ፡፡ ክብሬ ተስፋዬ በመድረክ መሪነት ትታወቃለች፡፡ በጦቢያ ዝግጅትና በቀደመ ስሙ ጣይቱ እና በአሁኑ ስሙ የእቴጌ እልፍኝ   በተሰኙ ሁለት ሴቶችና ሃገር ላይ በሚያተኩሩ ፕሮግራሞቿ ተመልካች በደንብ ያውቃታል፡፡ በሬዲዮ ፋና እርስዎ ቢሆኑ ምን ያደርጋሉ? በተሰኘው ተወዳጅ ፕሮግራምም የመጀመሪያዋ ሴት አወያይ በመሆን በሩን ለሴቶች ከፍታለች፡፡ ትውልድ ልጅነትና ትምህርት ጋዜጠኛ ክብሬ ተስፋዬ ህዳር 27 ቀን 1972 ዓ.ም ከአባቷ ከመምህር ተስፋዬ አበበ እና ከእናቷ ከወ/ሮ መሰለች ፈለቀ በአዲስ አበባ ከተማ በቂርቆስ ክፍለ...
ምስል
  ያዕቆብ ወልደማርያም    የመጀመርያው ኢትዮጵያዊ የኢትዮጵያን ሄራልድ   አዘጋጅ የመጀመርያው የኢትዮጵያን ሄራልድ ዋና አዘጋጅ አቶ ያእቆብ ወልደ ማርያም በአሁኑ ሰአት የ 93 አመት ሰው ናቸው፡፡ ይህ ጽሁፍ በተወዳጅ ሚድያ የፌስ ቡክ ገጽ እና ዊኪፒዲያ የወጣ እለት እሁድ ሰኔ 12 2014 93 አመት ይሞላቸዋል፡፡ ተወዳጅ ሚድያ ሀምሌ 30 2014 በሚያስመርቀው   መዝገበ-አእምሮ የ180 ሰዎች ታሪክ ውስጥ የአቶ ያእቆብ ታሪክ እንዲካተት ተደርጓል፡፡     በእንግሊዝኛ የጽሁፍ ችሎታቸው በሳል የሆኑት አቶ ያእቆብ ለተከታታይ 50 አመት በጋዜጠኝነት ሙያ በመቆየት ጠንካራ ባለሙያነታቸውን ያስመሰከሩ ናቸው፡፡   ሲሳይ ገብረ ማርያም እነሆ ታሪካቸውን እንደሚከተለው ሰንዶታል፡፡   አንጋፋው ጋዜጠኛ ያዕቆብ   ወልደማርያም፣ ከአባታቸው ከአቶ ወልደማርያም ሹባ ሌቃ፣ እንዲሁም ከእናታቸው ከወ / ሮ ወለተሚካኤል ሰንቤቶ ጋርባ እንደ አውሮጵያኖቹ አቆጣጠር ሰኔ 19 ቀን 1929 ዓ / ም በነቀምቴ ከተማ ተወለዱ።          የትምህርት ህይወት በነቀምት ተፈሪ መኮንን አንደኛ ደረጃ የመንግሥት ትምህርት ቤት ስለተቋቋመ እዚያ ገቡ፡፡ ይህን እንዳጠናቀቁ በአዲስ አበባ ኮተቤ የመጀመሪያው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከየክፍለ ሀገሩ ጥሩ ውጤት ያላቸው ተማሪዎች በፈተና ወደእዚህ ትምህርት ቤት እንዲገቡ ይደረግ ነበር። አቶ ያዕቆብም ፈተናውን በከፍተኛ ውጤት አልፈው ከስምንተኛ ክፍል ጀምሮ ዘመናዊ ት...